Wednesday, 26 August 2020 00:00

በሶሪያ  አዲስ የሐግያ ሶፊያ ቤተመቅደስ ሊገነባ ነው

Written by  በጋዜጠኛ ካሳሁን ለምለሙ

Overview

  በሩሲያ መንግሥት ድጋፍ በሶሪያ መለስተኛ የሆነ አዲስ የሐግያ ሶፊያ ቤተመቅደስ ሊገነባ እንደሆነ ኦርቶዶከስ ኮግኔት ፔጅ ዘግቧል፡፡ ቤተመቅደሱ የሚገነባው በርካታ የግሪክ  ኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን  በሚኖሩባት አል ሱቋአያላቢያህ ሲሆን ግንባታውም በቅርቡ ተጀምሮ በተያዘለት ጊዜ እንደሚጠናቀቅ ዘገባው አመልክቷል፡፡ በቱርክ የሚገኝው ጥንታዊውና ታሪካዊው  የሐግያ ሶፊያ ቤተመቅደስ ከርጅም ጊዜ በኋላ በቱርክ መንግሥት እምቢተኝነት የቤተመቅደሱ ይዘት በተወሰነ ደርጃ ተለውጦ በይፋ ወደ መስጅድነት ተቀይሮ ለሕዝበ ሙስሊሙ ማምለኪያነት እንደዋለም ዘገባው አስታውሷል፡፡  
Read 604 times